የግርጌ ማስታወሻ
a እርግጥ ነው፣ ዳንኤል ቃል በቃል አምላክን አላየውም። ከዚህ ይልቅ አምላክ፣ ዳንኤል በአእምሮው ውስጥ ጥርት ያለ ምስል እንዲታየው አድርጓል። ዳንኤል፣ የተመለከተውን ራእይ ለመግለጽ ለሰዎች የሚሠራባቸውን መግለጫዎች ተጠቅሟል። እነዚህ ዘይቤያዊ አገላለጾች አምላክን ሊገባን በሚችል መንገድ ለመግለጽ የተቀመጡ ናቸው፤ በመሆኑም እነዚህን መግለጫዎች ቃል በቃል ልንወስዳቸው አይገባም።