የግርጌ ማስታወሻ
b የጥንቶቹ ግብፃውያን ከ90 በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የዳቦና የኬክ ዓይነቶችን ይጋግሩ ነበር። በመሆኑም የፈርዖን የዳቦ ጋጋሪዎች አለቃ ከፍተኛ ሥልጣን ያለው ሰው ነበር። የመጠጥ አሳላፊዎቹ አለቃም ለፈርዖን የሚቀርበው ወይን ጠጅና እንደ ቢራ ያለ ሌላ መጠጥ ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆንና መርዝ እንዳይጨመርበት የመከታተል ኃላፊነት ነበረበት፤ ምክንያቱም በዚያ ዘመን በነገሥታት ላይ ሴራ መጠንሰስና የግድያ ሙከራ ማድረግ የተለመዱ ነገሮች ነበሩ። በመሆኑም የመጠጥ አሳላፊ ተደርጎ የሚሾመው ሰው አብዛኛውን ጊዜ የንጉሡ የቅርብ አማካሪ ነበር።