የግርጌ ማስታወሻ
b ተጨማሪ ማብራሪያ፦ መናፍስታዊ ድርጊቶች የሚባሉት ከአጋንንት ጋር ንክኪ ያላቸው ልማዶች ናቸው። እንዲህ ባለው ድርጊት የሚካፈሉ ግለሰቦች፣ የሞቱ ሰዎች መንፈስ በሕይወት መኖሩን እንደሚቀጥልና አብዛኛውን ጊዜ በመናፍስት ጠሪዎች አማካኝነት በሕይወት ካሉት ጋር ለመነጋገር እንደሚሞክር ያምናሉ። መናፍስታዊ ድርጊቶች እንደ ጥንቆላ፣ መተትና ሟርት ያሉትን ነገሮችም ያካትታሉ። አስማት የሚለው ቃል በዚህ ርዕስ ውስጥ የተሠራበት ከምትሃት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ድርጊቶች ለማመልከት ነው። በሰዎች ላይ ድግምት ማድረግንና ድግምት ማስፈታትንም ሊያካትት ይችላል። ቃሉ፣ አንዳንዶች ሌሎችን ለማዝናናት ብለው እጃቸውን በፍጥነት በማንቀሳቀስ የሚያሳዩትን ትርዒት አያመለክትም።