የግርጌ ማስታወሻ
c ሽማግሌዎች የመዝናኛ ምርጫን በተመለከተ ሕጎችን የማውጣት ሥልጣን አልተሰጣቸውም። እያንዳንዱ ክርስቲያን ከሚያነባቸውና ከሚመለከታቸው ነገሮች ወይም ከቪዲዮ ጨዋታዎች ጋር በተያያዘ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ የሠለጠነ ሕሊናውን ተጠቅሞ ውሳኔ ማድረግ አለበት። ጥበበኛ የሆኑ የቤተሰብ ራሶች የቤተሰባቸው መዝናኛ ከመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች ጋር የማይጋጭ እንዲሆን ጥረት ያደርጋሉ።—jw.org® ላይ የወጣውን “የይሖዋ ምሥክሮች አንዳንድ ፊልሞችን፣ መጻሕፍትን ወይም ዘፈኖችን ይከለክላሉ?” የሚል ርዕስ ተመልከት፤ ስለ እኛ > ብዙ ጊዜ የሚነሱ ጥያቄዎች በሚለው ሥር ይገኛል።