የግርጌ ማስታወሻ
b “ኪታዋላ” የሚለው መጠሪያ የመጣው “መቆጣጠር፣ መምራት ወይም መግዛት” የሚል ትርጉም ካለው የስዋሂሊ ቃል ነው። ኪታዋላ፣ ከቤልጅየም ቅኝ ግዛት ነፃ ለመውጣት የሚደረግ ፖለቲካዊ ንቅናቄ ነበር። የኪታዋላ ቡድኖች የይሖዋ ምሥክሮች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ይወስዱ፣ ያጠኑና ያሰራጩ ነበር፤ በተጨማሪም ፖለቲካዊ አመለካከታቸውን፣ በአጉል እምነት ላይ የተመሠረቱ ልማዶቻቸውን እንዲሁም ሥነ ምግባር የጎደለው አኗኗራቸውን ትክክል ለማስመሰል የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን አጣምመው ያቀርቡ ነበር።