የግርጌ ማስታወሻ
a ይሖዋን ለበርካታ ዓመታት ስናገለግል የቆየን ብንሆንም እንኳ የጎለመስንና የተሻልን ክርስቲያኖች ለመሆን ጥረት ማድረጋችንን መቀጠል እንፈልጋለን። ሐዋርያው ጳውሎስ የእምነት ባልንጀሮቹን ፈጽሞ ተስፋ እንዳይቆርጡ አበረታቷቸዋል! ለፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች የጻፈው ደብዳቤ፣ የሕይወትን ሩጫ በጽናት ለመሮጥ የሚረዳንን ማበረታቻ ይዟል። ይህ ርዕስ ጳውሎስ በመንፈስ መሪነት የተናገረውን ሐሳብ እንዴት ተግባራዊ ማድረግ እንደምንችል ያብራራል።