የግርጌ ማስታወሻ
b የሥዕሉ መግለጫ፦ ወንድሞች የስብሰባ አዳራሹን ሲያጸዱ ጆ የተባለው ወንድም ሥራውን ትቶ ከአንድ ወንድምና ከልጁ ጋር ማውራት ጀመረ። ምንጣፉን እያጸዳ ያለው ማይክ በዚህ ተበሳጨ። በመሆኑም ‘ቆሞ ማውራቱን ትቶ ሥራውን አይሠራም!’ ብሎ አሰበ። በኋላ ላይ ግን ጆ አንዲትን በዕድሜ የገፉ እህት በአሳቢነት ሲረዳቸው ማይክ ተመለከተ። ማይክ ይህን ሲመለከት፣ በወንድሙ ጥሩ ባሕርያት ላይ ይበልጥ ማተኮር እንዳለበት አስታወሰ።