የግርጌ ማስታወሻ
a አብዛኞቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች በሥራ 13:20 ላይ የተጠቀሰው “አራት መቶ ሃምሳ ዓመት” የመሳፍንትን ዘመን ሳይሆን ከዚያ በፊት የነበረውን ጊዜ እንደሚያመለክት ይናገራሉ። እነዚህ ዓመታት ይስሐቅ ከተወለደበት ከ1918 ከዘአበ አንስቶ የተስፋይቱ ምድር በ1467 ከዘአበ እስከተከፋፈለችበት ጊዜ ድረስ ያለውን የሚሸፍኑ ይመስላሉ። (ቅዱሳን ጽሑፎችን ጠለቅ ብሎ ማስተዋል ጥራዝ 1 ገጽ 462) በዕብራውያን 11:32 ላይ የተጠቀሱት መሳፍንት የተዘረዘሩበት ቅደም ተከተል መሳፍንት መጽሐፍ ውስጥ ካለው ቅደም ተከተል የተለየ ነው። ይሁን እንጂ ይህ በመሳፍንት መጽሐፍ ውስጥ የተዘገቡት ክንውኖች የጊዜ ቅደም ተከተላቸውን አልጠበቁም ለማለት የሚያስችል አይደለም። ሳሙኤል ከዳዊት በኋላ እንዳልመጣ የተረጋገጠ ነው።