የግርጌ ማስታወሻ
b ተጨማሪ ማብራሪያ፦ በመንፈስ ቅዱስ መቀባት። ይሖዋ በሰማይ ከኢየሱስ ጋር የሚገዙ ሰዎችን ለመምረጥ ቅዱስ መንፈሱን ይጠቀማል። አምላክ በመንፈሱ አማካኝነት ለእነዚህ ሰዎች ስለ ወደፊት ተስፋቸው “አስቀድሞ . . . ማረጋገጫ” ይሰጣቸዋል። (ኤፌ. 1:13, 14) እነዚህ ክርስቲያኖች ሰማያዊ ሽልማት ያላቸው መሆኑን መንፈስ ቅዱስ ‘እንደሚመሠክርላቸው’ ወይም ግልጽ እንደሚያደርግላቸው መናገር ይችላሉ።—ሮም 8:16