የግርጌ ማስታወሻ
a በዚህ ዓመት የክርስቶስ ሞት መታሰቢያ የሚከበረው ማክሰኞ፣ መጋቢት 29, 2012 ዓ.ም. (ሚያዝያ 7, 2020) ነው። በዚያ ምሽት ከምሳሌያዊው ቂጣና የወይን ጠጅ ለሚወስዱት ሰዎች ምን አመለካከት ሊኖረን ይገባል? የእነዚህ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ቢሄድ ጉዳዩ ሊያሳስበን ይገባል? ይህ ርዕስ ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ ሲሆን የተመሠረተው በጥር 2016 መጠበቂያ ግንብ ላይ በወጣ ትምህርት ላይ ነው።