የግርጌ ማስታወሻ
a ሐዋርያት ከኢየሱስ ጋር በመጨዋወትና በመሥራት የተወሰኑ ዓመታት አሳልፈዋል፤ ይህም ጥሩ ወዳጆች እንዲሆኑ አስችሏቸዋል። ኢየሱስ፣ እኛም ወዳጆቹ እንድንሆን ይፈልጋል፤ ሆኖም የእሱ ወዳጆች ለመሆን ጥረት ስናደርግ ሐዋርያቱ ያላጋጠሟቸው ተፈታታኝ ሁኔታዎች ያጋጥሙናል። ይህ ርዕስ አንዳንዶቹን ተፈታታኝ ሁኔታዎች ያብራራል፤ በተጨማሪም ከኢየሱስ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት መመሥረትና ይህን ወዳጅነት ጠብቀን ማቆየት የምንችልባቸውን እርምጃዎች ይገልጻል።