የግርጌ ማስታወሻ
a የምንኖረው የውሸት አባት የሆነው ሰይጣን በሚገዛው ዓለም ውስጥ ነው። በመሆኑም በእውነት ውስጥ መመላለስ ከፍተኛ ትግል ይጠይቅብናል። በመጀመሪያው መቶ ዘመን ዓ.ም. መገባደጃ ላይ ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያኖችም ተመሳሳይ ፈተና አጋጥሟቸው ነበር። ይሖዋ እነዚህን ክርስቲያኖችም ሆነ እኛን ለመርዳት ሲል ሐዋርያው ዮሐንስ ሦስት ደብዳቤዎችን እንዲጽፍ በመንፈሱ መርቶታል። እነዚህ ደብዳቤዎች የሚያጋጥሙንን እንቅፋቶች ለይተን ለማወቅ እንዲሁም ፈተናዎቹን ማሸነፍ የምንችልበትን መንገድ ለመገንዘብ ይረዱናል።