የግርጌ ማስታወሻ
a ከባድ መከራን በጽናት ስለተቋቋሙ ሰዎች ስናስብ መጀመሪያ ወደ አእምሯችን የሚመጣው ኢዮብ መሆን አለበት። ከዚያ ታማኝ ሰው ታሪክ ምን ትምህርት እናገኛለን? ሰይጣን ይሖዋን እንድንተው ሊያስገድደን እንደማይችል እንማራለን። ይሖዋ የሚያጋጥመንን ማንኛውንም ሁኔታ እንደሚያውቅም እንማራለን። በተጨማሪም ይሖዋ የኢዮብ መከራ እንዲያበቃ እንዳደረገ ሁሉ አንድ ቀን እኛንም ከመከራችን ሁሉ ይገላግለናል። በእነዚህ እውነታዎች ላይ ጠንካራ እምነት እንዳለን በተግባር ካሳየን ‘ይሖዋን ተስፋ አድርገናል’ ሊባል ይችላል።