የግርጌ ማስታወሻ
a በዛሬው ጊዜ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወንዶች፣ ሴቶችና ልጆች ምሥራቹን በቅንዓት እየሰበኩ ነው። አንተስ ከእነሱ መካከል ትገኛለህ? ከሆነ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመራር ሥር ሆነህ እየሠራህ ነው ማለት ነው። ኢየሱስ በዘመናችን የስብከቱን ሥራ እየመራው መሆኑን የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በዚህ ርዕስ ውስጥ እንመለከታለን። በዚህ ሐሳብ ላይ ማሰላሰላችን በክርስቶስ አመራር ሥር ሆነን ይሖዋን ማገልገላችንን ለመቀጠል ያነሳሳናል።