የግርጌ ማስታወሻ
a ይሖዋ የሚሰጠው ጥበብ፣ ዓለም ሊሰጠን ከሚችለው ከማንኛውም ነገር የላቀ ዋጋ አለው። በዚህ ርዕስ ላይ፣ በምሳሌ መጽሐፍ ውስጥ ስለሚገኝ ትኩረት የሚስብ አንድ ዘይቤያዊ አገላለጽ እንመለከታለን፤ የምሳሌ መጽሐፍ፣ ጥበብ በአደባባይ ላይ እንደምትጮኽ ይናገራል። እውነተኛ ጥበብ ማግኘት የምንችለው እንዴት እንደሆነ፣ አንዳንዶች ለጥበብ ጆሯቸውን ለመስጠት ፈቃደኛ የማይሆኑት ለምን እንደሆነ እንዲሁም ጥበብ ለምታሰማው ጥሪ ምላሽ መስጠታችን ምን ጥቅም እንደሚያስገኝልን እንመለከታለን።