የግርጌ ማስታወሻ
a ይሖዋ ስለ ወደፊቱ ጊዜ አስደናቂ ተስፋ ሰጥቶናል። ይህ ተስፋ ሕይወታችንን ብሩሕ የሚያደርግልን ከመሆኑም ሌላ በአሁኑ ጊዜ ከሚያጋጥሙን ፈተናዎች አሻግረን እንድንመለከት ይረዳናል። ምንም ዓይነት አስቸጋሪ ሁኔታ ቢያጋጥመን ታማኝነታችንን ለመጠበቅ የሚያስችል ብርታት ይሰጠናል። እንዲሁም አስተሳሰባችንን ሊመርዙ በሚችሉ ሐሳቦች ከመሸነፍ ይጠብቀናል። እነዚህ ምክንያቶች ክርስቲያናዊ ተስፋችንን እንድናጠናክር ያነሳሱናል። በዚህ ርዕስ ውስጥ ስለዚህ ጉዳይ እንመለከታለን።