የግርጌ ማስታወሻ
a በመታሰቢያው በዓል ሰሞን በኢየሱስ ሕይወትና ሞት እንዲሁም እሱና አባቱ ባሳዩን ፍቅር ላይ እንድናሰላስል ማበረታቻ ይሰጠናል። እንዲህ ማድረጋችን ለተግባር ያነሳሳናል። ይህ ርዕስ ለቤዛው ያለንን አድናቆት እንዲሁም ለይሖዋና ለኢየሱስ ያለንን ፍቅር ማሳየት የምንችልባቸውን አንዳንድ መንገዶች ያብራራል። ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን እንድንወድ፣ ድፍረት እንድናሳይ እንዲሁም በደስታ እንድናገለግል የሚያነሳሳን ምን እንደሆነም እናያለን።