የግርጌ ማስታወሻ
a በስብሰባዎች ላይ ሐሳብ ስንሰጥ እርስ በርስ እንበረታታለን። ይሁንና አንዳንዶች መልስ መመለስ ያስፈራቸዋል። ሌሎች ደግሞ መልስ መመለስ ቢያስደስታቸውም የሚፈልጉትን ያህል ዕድል እንደማይሰጣቸው ይሰማቸዋል። ያም ሆነ ይህ፣ ሁላችንም እንድንበረታታ አንዳችን ለሌላው አሳቢነት ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው? በተጨማሪም ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን ለፍቅርና ለመልካም ሥራ የሚያነቃቃ ሐሳብ መስጠት የምንችለው እንዴት ነው? በዚህ ርዕስ ውስጥ እነዚህን ጥያቄዎች እንመልሳለን።