የግርጌ ማስታወሻ
a በዛሬው ጊዜ ያሉ ብዙ ሰዎች አዲስ ዓለም እንደሚመጣ በሚገልጸው የመጽሐፍ ቅዱስ ተስፋ አያምኑም። ይህ ተስፋ የሕልም እንጀራ እንደሆነ ይሰማቸዋል። እኛ ግን ይሖዋ የሰጣቸው ተስፋዎች በሙሉ እንደሚፈጸሙ እርግጠኞች ነን። ያም ቢሆን እምነታችን ምንጊዜም ሕያው እንዲሆን ከፈለግን በቀጣይነት ልናጠናክረው ይገባል። ይህን ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው? ይህ ርዕስ መልሱን ይሰጠናል።