የግርጌ ማስታወሻ
a በቅርቡ እውነትን የሰማንም ሆንን ለበርካታ ዓመታት ይሖዋን ስናገለግል የቆየን፣ ሁላችንም እድገት ማድረጋችንን መቀጠል ያስፈልገናል። ይህ ርዕስ እንዲህ ማድረግ የምንችልበትን አንድ አስፈላጊ መንገድ ያብራራል፤ ይህም ለይሖዋና ለሌሎች ያለንን ፍቅር ማሳደግ ነው። በዚህ ርዕስ ላይ ስታሰላስል እስካሁን ያደረግኸውን እድገት ገምግም፤ እንዲሁም ተጨማሪ እድገት ማድረግ የምትችለው እንዴት እንደሆነ ለማሰብ ሞክር።