የግርጌ ማስታወሻ
a ሰይጣን ከአዳምና ከሔዋን ዘመን አንስቶ ሲያስፋፋ የቆየው አንድ ሐሳብ አለ፤ ይህም ‘ሰዎች ትክክልና ስህተት የሆነውን ነገር በራሳቸው የመወሰን መብት አላቸው’ የሚል ነው። እኛም ከይሖዋ ሕጎችና ከድርጅቱ ከሚሰጠን ማንኛውም መመሪያ ጋር በተያያዘ እንዲህ ዓይነት አመለካከት እንድናዳብር ይፈልጋል። ይህ ርዕስ የሰይጣን ዓለም የሚያስፋፋውን በራስ የመመራት መንፈስ ለመዋጋት ይረዳናል። ከይሖዋ ጎን ለመቆም ያለንን ቁርጠኝነትም ያጠናክርልናል።