የግርጌ ማስታወሻ
a በዛሬው ጊዜ ያሉ ወጣት የይሖዋ አገልጋዮች ድፍረታቸውንና ለይሖዋ ያላቸውን ታማኝነት የሚፈትኑ ሁኔታዎች ያጋጥሟቸዋል። በፍጥረት በማመናቸው የተነሳ አብረዋቸው የሚማሩ ልጆች ያሾፉባቸው ይሆናል። ወይም ደግሞ አምላክን በማገልገላቸውና በእሱ መሥፈርቶች በመመራታቸው የተነሳ እኩዮቻቸው ይሳለቁባቸው ይሆናል። ያም ቢሆን፣ በዚህ ርዕስ ውስጥ እንደምንመለከተው የነቢዩ ዳንኤልን ምሳሌ በመከተል ይሖዋን በድፍረትና በታማኝነት የሚያገለግሉ ሁሉ እውነተኛ ጥበብ አላቸው።