የግርጌ ማስታወሻ
b ዳንኤል የባቢሎናውያንን ምግብ ለመብላት ፈቃደኛ ያልሆነው በሚከተሉት ሦስት ምክንያቶች የተነሳ ሊሆን ይችላል፦ (1) የሚበሉት በሕጉ የተከለከሉትን እንስሳት ሥጋ ሊሆን ይችላል። (ዘዳ. 14:7, 8) (2) ሥጋው በተገቢው መንገድ ደሙ ያልፈሰሰ ሊሆን ይችላል። (ዘሌ. 17:10-12) (3) ምግቡን መብላቱ የጣዖት አምልኮ ተካፋይ እንደሆነ ሊያስቆጥረው ይችላል።—ከዘሌዋውያን 7:15፤ 1 ቆሮንቶስ 10:18, 21, 22 ጋር አወዳድር።