የግርጌ ማስታወሻ
a በዓለም ላይ ያለው ሁኔታ እየተባባሰ ቢሄድም እንኳ የወደፊቱ ሕይወታችን አስደሳች እንደሚሆን መተማመን እንችላለን። የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶችን ማጥናታችን ስለዚህ ጉዳይ እርግጠኞች እንድንሆን ይረዳናል። ይህ ርዕስ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶችን መመርመር ያለብን ለምን እንደሆነ በዝርዝር ያብራራል። በተጨማሪም ዳንኤል የጻፋቸውን ሁለት ትንቢቶች በአጭሩ እንመለከታለን፤ እንዲሁም እነዚህን ትንቢቶች መመርመራችን በግለሰብ ደረጃ ጥቅም የሚያስገኝልን እንዴት እንደሆነ እናያለን።