የግርጌ ማስታወሻ
d ንጉሥ አሳ ከባድ ኃጢአቶችን ፈጽሟል። (2 ዜና 16:7, 10) ያም ቢሆን መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሰው በአዎንታዊ መንገድ ነው። የተሰጠውን እርማት መጀመሪያ ላይ ባይቀበልም ከጊዜ በኋላ ንስሐ ገብቶ ሊሆን ይችላል። በጥቅሉ ሲታይ መልካም ባሕርያቱ ከስህተቶቹ ይበልጡ ነበር። አሳ ይሖዋን ብቻ ማምለኩን እንዲሁም ከመንግሥቱ የጣዖት አምልኮን ለማስወገድ ጥረት ማድረጉን ልብ ማለት ያስፈልጋል።—1 ነገ. 15:11-13፤ 2 ዜና 14:2-5