የግርጌ ማስታወሻ
b ጳውሎስ በኤፌሶን 1:10 ላይ “በሰማያት የሚሆኑ ነገሮችን” ስለመሰብሰብ የተናገረው ሐሳብ ኢየሱስ በማቴዎስ 24:31 እና በማርቆስ 13:27 ላይ “የተመረጡትን” ስለመሰብሰብ ከተናገረው ሐሳብ የተለየ ነው። ጳውሎስ የተናገረው ይሖዋ መንፈሳዊ ልጆቹን በመንፈስ ቅዱስ በመቀባት ስለሚመርጥበት ጊዜ ነው። ኢየሱስ የተናገረው ደግሞ በምድር ላይ የቀሩት ቅቡዓን ክርስቲያኖች በታላቁ መከራ ወቅት ወደ ሰማይ ስለሚሰበሰቡበት ጊዜ ነው።