የግርጌ ማስታወሻ
a መላእክትም ይሖዋን ወክለው በእሱ ስም ለሰዎች መልእክት ያስተላለፉበት ጊዜ አለ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንዳንድ ሐሳቦችን የተናገሩት መላእክት ሆነው ሳለ ይሖዋ ራሱ እንደተናገረ ተደርጎ የተገለጸው ለዚህ ነው። (ዘፍ. 18:1-33) ቅዱሳን መጻሕፍት ሙሴ ሕጉን የተቀበለው ከይሖዋ እንደሆነ ቢናገሩም ሌሎች ጥቅሶች ደግሞ ይሖዋ በእሱ ስም ሕጉን እንዲያስተላልፉ መላእክትን እንደተጠቀመ ይገልጻሉ።—ዘሌ. 27:34፤ ሥራ 7:38, 53፤ ገላ. 3:19፤ ዕብ. 2:2-4