የግርጌ ማስታወሻ
c ለምሳሌ ያህል፣ በአሜሪካ የሚገኙ በፕሮቴስታንት ሥር የሚታቀፉ በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን የሚወክል ምክር ቤት፣ የቃል ኪዳኑ ማኅበር “የአምላክን መንግሥት በምድር ላይ የሚወክል ፖለቲካዊ ምልክት” እንደሆነ በ1918 ገልጾ ነበር። በ1965 የሂንዱይዝም፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ፣ የቡድሂዝም፣ የአይሁድ፣ የእስልምና፣ የካቶሊክና የፕሮቴስታንት እምነት ተወካዮች ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለመጸለይ በሳን ፍራንሲስኮ ተሰብስበው ነበር። በ1979 ደግሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዳግማዊ ጆን ፖል፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት “ከፍተኛው የሰላምና የፍትሕ መድረክ ሆኖ እንዲቀጥል” ያላቸውን ምኞት ገልጸዋል።