የግርጌ ማስታወሻ
a አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ኢሳይያስ 14:12 ላይ “ሉሲፈር” የሚለውን ቃል የሚጠቀሙ ሲሆን፤ ብዙዎች ይህ መጠሪያ ሰይጣን ዲያብሎስ መልአክ በነበረበት ወቅት ይጠራበት የነበረው ስም እንደሆነ ይሰማቸዋል። ሆኖም እዚህ ጥቅስ ላይ የተሠራበት የዕብራይስጥ ቃል ትርጉሙ ‘የሚያበራ ኮከብ’ ማለት ነው። ከጥቅሱ አገባብ መረዳት እንደሚቻለው ይህ አጠራር የሚያመለክተው ሰይጣንን ሳይሆን እብሪተኛ በመሆኑ ምክንያት አምላክ የሚያዋርደውን የባቢሎንን ሥርወ መንግሥት ነው። (ኢሳይያስ 14:4, 13-20) ‘የሚያበራ ኮከብ’ የሚለው አገላለጽ የባቢሎን ሥርወ መንግሥት ከወደቀ በኋላ የሚኖረውን ሁኔታ ለመግለጽ የገባ የምጸት አነጋገር ነው።