የግርጌ ማስታወሻ
a መጽሐፍ ቅዱስ አምላክ “ክብ ከሆነችው ምድር በላይ ይኖራል” ሲል ይናገራል። (ኢሳይያስ 40:22) አንዳንድ የማመሣከሪያ ጽሑፎች እዚህ ጥቅስ ላይ “ክብ” ተብሎ የተተረጎመው ቃል ድቡልቡል የሚል ትርጉም ሊኖረው እንደሚችል ይገልጻሉ፤ እርግጥ በዚህ ሐሳብ የሚስማሙት ሁሉም ምሁራን አይደሉም። ያም ሆነ ይህ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ምድር ጠፍጣፋ እንደሆነች የሚገልጸውን ሐሳብ አይደግፍም።