የግርጌ ማስታወሻ
a ዮናታን ለመጀመሪያ ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሰው ሳኦል መግዛት በጀመረበት ወቅት ነው፤ ዮናታን በወቅቱ የጦር አዛዥ ስለነበር ዕድሜው ቢያንስ 20 ዓመት መሆን ይኖርበታል። (ዘኁልቁ 1:3፤ 1 ሳሙኤል 13:2) ሳኦል ለ40 ዓመታት ገዝቷል። በመሆኑም ሳኦል ሲሞት ዮናታን 60 ዓመት ገደማ፣ ዳዊት ደግሞ 30 ዓመቱ ነበር። (1 ሳሙኤል 31:2፤ 2 ሳሙኤል 5:4) በመሆኑም ዮናታን ዳዊትን በ30 ዓመት ገደማ ሳይበልጠው አይቀርም።