የግርጌ ማስታወሻ
b ክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች የአምላክ ስም ከሚገኝባቸው “የብሉይ ኪዳን” ክፍሎች ላይ ሲጠቅሱ ስሙን ሳይጠቀሙ አልቀሩም። ዚ አንከር ባይብል ዲክሽነሪ እንዲህ ብሏል፦ “የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት መጀመሪያ ላይ በተጻፉበት ጊዜ፣ በአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ባሉ ከብሉይ ኪዳን የተወሰዱ የተወሰኑ ወይም ሁሉም ጥቅሶች ላይ ያህዌህ የሚለውን መለኮታዊ ስም የሚወክለው ቴትራግራማተን ይገኝ እንደነበር አንዳንድ ማስረጃዎች ይጠቁማሉ።” (ጥራዝ 6፣ ገጽ 392) ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት አዲስ ዓለም ትርጉም በተባለው መጽሐፍ ቅዱስ ተጨማሪ መረጃ ሀ5 ላይ የሚገኘውን “መለኮታዊው ስም በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ” የሚለውን ርዕስ ተመልከት። ሮም 10:13 ላይ የአምላክን ስም የሚጠቀሙ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞችን ዝርዝር አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ የጥናት እትም (እንግሊዝኛ) ላይ ማግኘት ትችላለህ።