የግርጌ ማስታወሻ
c አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም እንደገለጸው በዚህ ጥቅስ ላይ የአምላክ ስም የተደጋገመው “ለማጉላትና [ቁጥር 27] ላይ ለሚገኘው ሐሳብ ክብደት ለመስጠት ነው።” ይሁንና አንዳንዶች የአምላክ ስም ሦስት ጊዜ መጠቀሱ የሥላሴን ትምህርት የሚደግፍ እንደሆነ ይናገራሉ። ይህ ግን ትክክል አይደለም። ሥላሴን የሚደግፍ አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኝ ጽሑፍ እንዲህ ሲል ሐቁን ተቀብሏል፦ የአምላክ ስም ሦስት ጊዜ መጠቀሱ “ቃለ ቡራኬውን ለሚሰጠው ካህንም ሆነ ለተቀባዩ ሕዝብ እንዲህ ያለ መልእክት ሊያስተላልፍ አይችልም። ሦስቴ መጠቀሱ ለቃለ ቡራኬው ውበትና ሙላት ከመጨመር ውጭ ለእነሱ የሚያስተላልፈው ትርጉም የለም።” (ዘ ፑልፒት ኮሜንታሪ፣ ጥራዝ 2፣ ገጽ 52) ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት “አምላክ ሥላሴ ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።