መዝሙር 115
አምላክ ላሳየን ትዕግሥት አመስጋኝ መሆን
በወረቀት የሚታተመው
1. አምላካችን፣ ታላቅ ነው ኃይልህ፤
ጽድቅን እጅግ ትወዳለህ።
ግን በምድር ክፋት ነግሷል፤
ልባችንም በጣም አዝኗል።
አትዘገይም፣ ለሰው ባይመስልም፤
ክፋት ይጠፋል፤ ጊዜው ቀርቧል።
(አዝማች)
አንተን ተስፋ ’ናደርጋለን፤
ስምህንም እናውጃለን።
2. እናውቃለን ሺህ ዓመት ላንተ፤
እንዳንድ ቀን እንደሆነ።
ታላቁ ቀንህ ይመጣል፤
አይዘገይም፣ ጊዜው ቀርቧል።
ኃጢያትን ሁሉ ብትጠላም፣
ሰው ሲመለስ ግን ደስ ይልሃል።
(አዝማች)
አንተን ተስፋ ’ናደርጋለን፤
ስምህንም እናውጃለን።
(በተጨማሪም ነህ. 9:30ን፣ ሉቃስ 15:7ን እና 2 ጴጥ. 3:8, 9ን ተመልከት።)