-
ለዘመናዊው ኑሮ ተግባራዊ ጥቅም የሚሰጥ መጽሐፍለሰው ሁሉ የሚሆን መጽሐፍ
-
-
መጽሐፍ ቅዱስ ግን ስለ ጋብቻ ሚዛኑን የጠበቀና አስተማማኝ የሆነ ምክር ሲሰጥ ቆይቷል። በአንዳንድ ከበድ ያሉ ሁኔታዎች መፋታት እንደሚፈቀድ ይናገራል። (ማቴዎስ 19:9) ቢሆንም በየጥቃቅኑ ምክንያት መፋታትን ያወግዛል። (ሚልክያስ 2:14-16) በተጨማሪም በጋብቻ ላይ መወስለትን ያወግዛል። (ዕብራውያን 13:4) ጋብቻ የእርስ በርስ መተሳሰር እንደሆነ ይናገራል። “ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፣ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ይሆናሉ” ይላል።a—ዘፍጥረት 2:24፤ ጋደል አድርገን የጻፍነው እኛ ነን፤ ማቴዎስ 19:5, 6
-
-
ለዘመናዊው ኑሮ ተግባራዊ ጥቅም የሚሰጥ መጽሐፍለሰው ሁሉ የሚሆን መጽሐፍ
-
-
a እዚህ ላይ ‘መጣበቅ’ ተብሎ የተተረጎመው ዳቫቅ የተባለ የዕብራይስጥ ቃል “ከአንድ ሰው ጋር በፍቅርና በታማኝነት መጣበቅን ያመለክታል።”4 ማቴዎስ 19:5 ላይ “ይጣበቃል” ተብሎ የተተረጎመው የግሪክኛ ቃል “በሙጫ ወይም በሲሚንቶ ማጣበቅን” ወይም ደግሞ “አንድ ላይ አጥብቆ ማያያዝን” ከሚያመለክት ቃል ጋር ይዛመዳል።5
-