-
አምላክ መከራና ሥቃይ እንዲኖር የፈቀደው ለምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—2014 | ጥር 1
-
-
ሐና፦ እሺ። “እባብ እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠራቸው የዱር አራዊት ሁሉ ተንኰለኛ ነበረ፤ ሴቲቱንም፣ ‘በእርግጥ እግዚአብሔር፣ “በአትክልቱ ስፍራ ካሉ ዛፎች ከማናቸውም እንዳትበሉ” ብሎአልን?’ አላት። ሴቲቱም እባቡን እንዲህ አለችው፤ ‘በአትክልቱ ስፍራ ካሉት ዛፎች ፍሬ መብላት እንችላለን፤ ነገር ግን እግዚአብሔር “በአትክልቱ ስፍራ መካከል ከሚገኘው ዛፍ ፍሬ እንዳትበሉ፤ እንዳትነኩትም፤ አለበለዚያ ትሞታላችሁ” ብሎአል።’ እባቡም ሴቲቱን እንዲህ አላት፤ ‘መሞት እንኳ አትሞቱም፤ ከፍሬው በበላችሁ ጊዜ ዐይናችሁ እንደሚከፈትና መልካምና ክፉን በማወቅ፣ እንደ እግዚአብሔር እንደምትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው።’”
-
-
አምላክ መከራና ሥቃይ እንዲኖር የፈቀደው ለምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—2014 | ጥር 1
-
-
ዮሐና፦ ትክክል ነሽ። ሰይጣን ቀጥሎ የተናገረው ነገር በአምላክ ላይ የተሰነዘረ ትልቅ ክስ ነው። “መሞት እንኳ አትሞቱም” እንዳላቸው ልብ በይ። ሰይጣን እንዲህ ሲል አምላክ ውሸታም እንደሆነ መናገሩ ነበር!
ሐና፦ ይህን ልብ ብየው አላውቅም ነበር።
ዮሐና፦ ሰይጣን፣ አምላክ ውሸታም እንደሆነ በመናገር የሰነዘረው ክስ ትክክል መሆን አለመሆኑ እንዲረጋገጥ ከተፈለገ ጊዜ ይጠይቃል። እንዲህ ያልኩሽ ለምን እንደሆነ ገብቶሻል?
ሐና፦ አይ፣ በደንብ አልገባኝም።
ዮሐና፦ ነጥቡ ይበልጥ ግልጽ እንዲሆንልሽ አንድ ምሳሌ ልንገርሽ። እኔ ከአንቺ ይበልጥ ጠንካራ ነኝ በማለት ተፎካከርኩሽ እንበል። ማናችን ይበልጥ ጠንካራ እንደሆንን ማረጋገጥ የሚቻለው እንዴት ነው ትያለሽ?
ሐና፦ ምናልባት ሁለታችንም ጉልበታችንን የሚፈትን ነገር በማድረግ ማን ጠንካራ መሆኑን ማሳየት እንችል ይሆናል።
ዮሐና፦ እውነትሽን ነው። ምናልባትም አንድ ከባድ ዕቃ መርጠን ማናችን ማንሳት እንደምንችል መሞከር ሊሆን ይችላል። እንደ እውነቱ ከሆነ ማን ጠንካራ ነው የሚለውን መለየት ያን ያህል አስቸጋሪ አይደለም።
ሐና፦ ምን ለማለት እንደፈለግሽ ገብቶኛል።
ዮሐና፦ ሆኖም ከአንቺ ይበልጥ ጠንካራ ነኝ ከማለት ይልቅ ከአንቺ ይበልጥ ሐቀኛ እንደሆንኩ አድርጌ ብናገርስ? ይህን ማረጋገጥ ይበልጥ አስቸጋሪ የሚሆን አይመስልሽም?
ሐና፦ ልክ ነሽ፣ አስቸጋሪ ይመስለኛል።
ዮሐና፦ ሐቀኝነት ልክ እንደ ጥንካሬ በቀላል ሙከራ ሊረጋገጥ የሚችል ነገር አይደለም።
ሐና፦ እውነትሽን ነው።
ዮሐና፦ ስለዚህ ሰዎች ከሁለታችን ማናችን ሐቀኛ እንደሆንን ማረጋገጥ የሚችሉት በቂ ጊዜ ተሰጥቷቸው አኗኗራችንን ማየት ከቻሉ ብቻ ነው።
ሐና፦ ይህ ምክንያታዊ ይመስላል።
ዮሐና፦ እስቲ በዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ ያለውን ዘገባ መለስ ብለሽ ተመልከቺው። ታዲያ ሰይጣን ከአምላክ ይበልጥ ኃይል እንዳለው ነው የተናገረው?
ሐና፦ አይደለም።
ዮሐና፦ ያ ቢሆን ኖሮ አምላክ፣ ሰይጣን ሐሰተኛ መሆኑን በቀላሉ ማሳየት ይችል ነበር። ሆኖም ሰይጣን የተናገረው ከአምላክ ይልቅ እሱ ሐቀኛ እንደሆነ ነው። ሰይጣን ሔዋንን ‘አምላክ ዋሽቷችኋል፤ እኔ ግን እውነቱን እየነገርኩሽ ነው’ ያላት ያህል ነበር።
ሐና፦ በጣም ይገርማል።
ዮሐና፦ ጥበበኛ የሆነው አምላክ ይህ ጉዳይ እልባት እንዲያገኝ በቂ ጊዜ ፈቀደ። ማን ሐቀኛና ማን ውሸታም እንደሆነ በጊዜ ሂደት መታወቁ አይቀርም።
-