-
አምላክ መከራና ሥቃይ እንዲኖር የፈቀደው ለምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—2014 | ጥር 1
-
-
ሐና፦ እሺ። “እባብ እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠራቸው የዱር አራዊት ሁሉ ተንኰለኛ ነበረ፤ ሴቲቱንም፣ ‘በእርግጥ እግዚአብሔር፣ “በአትክልቱ ስፍራ ካሉ ዛፎች ከማናቸውም እንዳትበሉ” ብሎአልን?’ አላት። ሴቲቱም እባቡን እንዲህ አለችው፤ ‘በአትክልቱ ስፍራ ካሉት ዛፎች ፍሬ መብላት እንችላለን፤ ነገር ግን እግዚአብሔር “በአትክልቱ ስፍራ መካከል ከሚገኘው ዛፍ ፍሬ እንዳትበሉ፤ እንዳትነኩትም፤ አለበለዚያ ትሞታላችሁ” ብሎአል።’ እባቡም ሴቲቱን እንዲህ አላት፤ ‘መሞት እንኳ አትሞቱም፤ ከፍሬው በበላችሁ ጊዜ ዐይናችሁ እንደሚከፈትና መልካምና ክፉን በማወቅ፣ እንደ እግዚአብሔር እንደምትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው።’”
-
-
አምላክ መከራና ሥቃይ እንዲኖር የፈቀደው ለምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—2014 | ጥር 1
-
-
ዮሐና፦ በተወሰነ ደረጃ ተረጋግጧል። ይሁንና ሰይጣን የሰነዘረው ክስ ይህ ብቻ አልነበረም። እስቲ ቁጥር 5ን እንደገና ተመልከቺው። እዚህ ላይ ሰይጣን ሔዋንን ምን ሌላ ተጨማሪ ነገር እንደነገራት ልብ ብለሻል?
ሐና፦ ከፍሬው ከበላች ዓይኖቿ እንደሚገለጡ ነግሯታል።
ዮሐና፦ ልክ ነሽ፤ እንዲያውም ‘መልካምና ክፉን በማወቅ እንደ አምላክ እንደሚሆኑ’ ነግሯታል። ስለዚህ ሰይጣን፣ አምላክ የሰው ልጆችን አንድ መልካም ነገር እንዳስቀረባቸው አድርጎ ተናግሯል።
ሐና፦ አሃ፣ አሁን ገባኝ።
ዮሐና፦ ይህም ቢሆን መልስ የሚያሻው ወሳኝ ጥያቄ ነው።
ሐና፦ ምን ማለትሽ ነው?
ዮሐና፦ ሰይጣን እንዲህ ብሎ ሲናገር ሔዋንን ማለትም የሰው ልጆችን አምላክ ከሚገዛቸው ይልቅ ራሳቸውን በራሳቸው ቢያስተዳድሩ የተሻለ ነው ማለቱ ነበር። ይሖዋ ይህ ጥያቄም ቢሆን በተሻለ ሁኔታ መልስ እንዲያገኝ ማድረግ የሚቻለው ሰይጣን የተናገረው ነገር ትክክል መሆን አለመሆኑ እንዲረጋገጥ ጊዜ በመፍቀድ እንደሆነ ያውቃል። ስለሆነም አምላክ፣ ሰይጣን ይህን ዓለም ለተወሰነ ጊዜ እንዲገዛ ፈቀደለት። ይህ ሁሉ መከራ እየደረሰብን ያለውም ለዚህ ነው፤ ይህን ዓለም እየገዛ ያለው አምላክ ሳይሆን ሰይጣን ነው።d ይሁንና አንድ የምሥራች አለ።
-