-
ይሖዋ ‘ሚስጥር ገላጭ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 15
-
-
4. የሴቲቱ ዘር ክፍል እነማን ናቸው? ይህ ዘርስ ምን ነገር ያከናውናል?
4 በኤደን ዓመፅ ከተነሳ በኋላ ወዲያውኑ ይሖዋ ‘ሴቲቱ ዘር’ እንደምታስገኝ ቃል ገባ።a (ዘፍጥረት 3:15ን አንብብ።) የሴቲቱ ዘር ወደፊት የእባቡን ማለትም የሰይጣንን ራስ ይቀጠቅጣል። ይህ ዘር በአብርሃም በኩል እንደሚመጣ፣ ከእስራኤል ብሔር ወገን እንደሚሆን እንዲሁም በይሁዳ የዘር ሐረግና በንጉሥ ዳዊት የትውልድ መስመር በኩል እንደሚመጣ ይሖዋ ከጊዜ በኋላ አሳውቋል። (ዘፍ. 22:15-18፤ 49:10፤ መዝ. 89:3, 4፤ ሉቃስ 1:30-33) በኋላም የዚህ ዘር ዋነኛ ክፍል ክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ ተገኘ። (ገላ. 3:16) በመንፈስ የተቀቡ የክርስቲያን ጉባኤ አባላት ደግሞ የዘሩ ሁለተኛ ክፍል ሆኑ። (ገላ. 3:26-29) ኢየሱስና ቅቡዓኑ በአንድነት የአምላክን መንግሥት ይመሠርታሉ፤ አምላክም ሰይጣንን ለመቀጥቀጥ ይህን መንግሥት መሣሪያ አድርጎ ይጠቀምበታል።—ሉቃስ 12:32፤ ሮም 16:20
5, 6. (ሀ) ዳንኤልና ዮሐንስ የጠቀሱት ስንት ኃያላን መንግሥታትን ነው? (ለ) በራእይ መጽሐፍ ላይ የተጠቀሰው አውሬ ራሶች ምን ያመለክታሉ?
5 በኤደን የተነገረው የመጀመሪያው ትንቢት ሰይጣንም የራሱን “ዘር” እንደሚያስገኝ ይገልጻል። ይህ ዘር፣ ለሴቲቱ ዘር ጠላትነት እንደሚኖረውም ያሳያል። ለመሆኑ የእባቡ ዘር ክፍል እነማን ናቸው? የሰይጣንን መንገድ በመከተል አምላክን የሚጠሉና ሕዝቡን የሚቃወሙ ሁሉ ከእባቡ ዘር ክፍል ይመደባሉ። በታሪክ ዘመናት ሁሉ ሰይጣን በተለያዩ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ወይም መንግሥታት አማካኝነት ዘሩን ሲያደራጅ ቆይቷል። (ሉቃስ 4:5, 6) ይሁን እንጂ በአምላክ ሕዝቦች ይኸውም በእስራኤል ብሔርም ሆነ በቅቡዓን ክርስቲያኖች ጉባኤ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳደሩት ሰብዓዊ መንግሥታት በጣም ጥቂት ናቸው። ይህን ሐቅ ማወቃችን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ዳንኤልና ዮሐንስ በተመለከቷቸው ራእዮች ላይ ስምንት ኃያላን መንግሥታት ብቻ የተጠቀሱት ለምን እንደሆነ ግልጽ ስለሚያደርግልን ነው።
-
-
ይሖዋ ‘ሚስጥር ገላጭ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 15
-
-
7. የመጀመሪያው ራስ የሚወክለው ማንን ነው? ለምንስ?
7 የአውሬው የመጀመሪያ ራስ ግብፅን ይወክላል። እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው? ምክንያቱም ለአምላክ ሕዝቦች ጠላትነት ያሳየችው የመጀመሪያዋ ኃያል መንግሥት ግብፅ ነበረች። የሴቲቱ ዘር መገኛ የሆኑት የአብርሃም ዘሮች በግብፅ ቁጥራቸው እጅግ እየበዛ ሄዶ ነበር። በዚህ ጊዜ የግብፅ መንግሥት እስራኤላውያንን መጨቆን ጀመረ። ሰይጣን የሴቲቱ ዘር ከመምጣቱ በፊት የአምላክን ሕዝብ ጨርሶ ለማጥፋት ሞክሮ ነበር። እንዴት? እስራኤላዊ የሆኑ ወንድ ሕፃናትን እንዲገድል ፈርዖንን በማነሳሳት ነው። ይሖዋ ግን ይህ የሰይጣን እቅድ እንዲከሽፍ ያደረገ ሲሆን ሕዝቡንም ከግብፅ ባርነት ነፃ አውጥቷቸዋል። (ዘፀ. 1:15-20፤ 14:13) ከጊዜ በኋላም እስራኤላውያን ተስፋይቱን ምድር እንዲወርሱ አድርጓቸዋል።
8. ሁለተኛው ራስ የሚወክለው ማንን ነው? ምን ሙከራስ አድርጓል?
8 የአውሬው ሁለተኛ ራስ ደግሞ አሦርን ይወክላል። ይህ ኃያል መንግሥትም ቢሆን የአምላክን ሕዝቦች ጠራርጎ ለማጥፋት ሙከራ አድርጓል። እርግጥ ነው፣ አሥሩን ነገድ ያቀፈው የእስራኤል መንግሥት ወደ ጣዖት አምልኮ ዘወር ባለበትና ባመፀበት ወቅት ይሖዋ የአሦርን መንግሥት ተጠቅሞ ቀጥቶት ነበር። ይሁንና አሦር በኢየሩሳሌም ላይ ጥቃት ሰነዘረ። በዚህ ወቅት ሰይጣን፣ ኢየሱስ የሚመጣበትን ንጉሣዊ የዘር ሐረግ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት አስቦ ሊሆን ይችላል። አሦር በኢየሩሳሌም ላይ ጥቃት እንዲሰነዝር ግን ይሖዋ አልፈለገም፤ በመሆኑም ይሖዋ ይህን ወራሪ ጠላት በማጥፋት ታማኝ ሕዝቦቹን ተአምራዊ በሆነ መንገድ አድኗቸዋል።—2 ነገ. 19:32-35፤ ኢሳ. 10:5, 6, 12-15
-
-
ይሖዋ ‘ሚስጥር ገላጭ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 15
-
-
13 ይሖዋ በትንቢት ባስነገረው መሠረት ባቢሎናውያንን ለመገልበጥና እስራኤላውያንን ወደ ትውልድ አገራቸው ለመመለስ ሜዶ ፋርስን ተጠቅሟል። (2 ዜና 36:22, 23) ይሁንና ይህ መንግሥት ከጊዜ በኋላ የአምላክን ሕዝብ ለማጥፋት ተቃርቦ ነበር። የፋርስ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበረው ሐማ አይሁዳውያንን ለማጥፋት ሴራ ጠንስሶ እንደነበር የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የሆነው የአስቴር መጽሐፍ ዘግቧል። ሐማ፣ ሰፊ በሆነው የፋርስ ግዛት ውስጥ የሚገኙትን አይሁዳውያን በሙሉ ለማጥፋት ዝግጅት አድርጎ የነበረ ሲሆን ይህን የዘር ማጥፋት ዘመቻ የሚያደርግበትን ቀን ጭምር ወስኖ ነበር። በዚህ ወቅትም ቢሆን የአምላክ ሕዝቦች የሰይጣን ዘር ከሰነዘረባቸው ጥቃት ማምለጥ የቻሉት ይሖዋ ጣልቃ ስለገባ ነው። (አስ. 1:1-3፤ 3:8, 9፤ 8:3, 9-14) በመሆኑም የሜዶ ፋርስ መንግሥት በራእይ መጽሐፍ ላይ በተገለጸው አውሬ አራተኛ ራስ መወከሉ የተገባ ነው።
-
-
ይሖዋ ‘ሚስጥር ገላጭ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 15
-
-
16. አንታይከስ አራተኛ ምን አድርጓል?
16 የግሪክ መንግሥት ፋርስን ድል ካደረገ በኋላ የአምላክ ሕዝቦች ይኖሩበት የነበረውን አካባቢ ተቆጣጠረ። በዚህ ወቅት አይሁዳውያን ወደ ተስፋይቱ ምድር የተመለሱ ሲሆን በኢየሩሳሌም የሚገኘውን ቤተ መቅደስ እንደገና ገነቡ። በዚህ ጊዜም ቢሆን አይሁዳውያን የአምላክ የተመረጡ ሕዝቦች ነበሩ፤ እንዲሁም ቤተ መቅደሱ የእውነተኛው አምልኮ ማዕከል መሆኑን ቀጥሎ ነበር። ሆኖም በሁለተኛው መቶ ዘመን ዓ.ዓ. የአውሬው አምስተኛ ራስ የሆነው ግሪክ በአምላክ ሕዝቦች ላይ ጥቃት ሰነዘረ። ከተከፋፈለው የእስክንድር ግዛት ውስጥ ከተነሱት ነገሥታት አንዱ የሆነው አንታይከስ አራተኛ ኢየሩሳሌም በሚገኘው ቤተ መቅደስ ውስጥ የጣዖት መሰዊያ ያቆመ ከመሆኑም በላይ የአይሁድን እምነት መከተል በሞት የሚያስቀጣ ወንጀል እንደሆነ የሚናገር አዋጅ አወጣ። ይህም ቢሆን የሰይጣን ዘር ክፍል ጠላትነቱን የገለጸበት ድርጊት ነው። ብዙም ሳይቆይ ግሪክ በሌላ የዓለም ኃያል መንግሥት ተተካ። ታዲያ የአውሬው ስድስተኛ ራስ የሚሆነው ማን ነው?
-
-
ይሖዋ ‘ሚስጥር ገላጭ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 15
-
-
17. ስድስተኛው ራስ በዘፍጥረት 3:15 የሚገኘው ትንቢት እንዲፈጸም ምን ጉልህ ሚና ተጫውቷል?
17 ዮሐንስ ስለ አውሬው ራእይ በተመለከተበት ወቅት የዓለም ኃያል መንግሥት የነበረው ሮም ነው። (ራእይ 17:10) የአውሬው ስድስተኛ ራስ በዘፍጥረት 3:15 ላይ የሚገኘው ትንቢት እንዲፈጸም ጉልህ ሚና ተጫውቷል። ሰይጣን የሮም ባለሥልጣናትን በመጠቀም የዘሩን ‘ተረከዝ’ ስለቀጠቀጠ በሴቲቱ ዘር ላይ ጊዜያዊ ጉዳት አድርሶ ነበር። ሮማውያን ይህን ያደረጉት በመንግሥት ላይ ዓመፅ ያነሳሳል በሚል ኢየሱስን በሐሰት ክስ በመወንጀልና በመግደል ነው። (ማቴ. 27:26) ይሁን እንጂ ይሖዋ ኢየሱስን ከሞት ሲያስነሳው በዘሩ ተረከዝ ላይ የነበረው ቁስል ወዲያውኑ ዳነ።
18. (ሀ) ይሖዋ የመረጠው አዲስ ብሔር የትኛው ነው? ለምንስ? (ለ) የእባቡ ዘር ለሴቲቱ ዘር ጠላትነቱን ማሳየቱን የቀጠለው እንዴት ነው?
18 የእስራኤል ሃይማኖታዊ መሪዎች ኢየሱስን በመቃወም ከሮም መንግሥት ጋር የተመሳጠሩ ሲሆን አብዛኛው ሕዝብም መሲሑን አልተቀበለውም። በመሆኑም ሥጋዊ እስራኤላውያን የይሖዋ ሕዝብ የመሆን መብታቸውን አጡ። (ማቴ. 23:38፤ ሥራ 2:22, 23) ይሖዋም በእነሱ ምትክ አዲስ ብሔር ይኸውም ‘የአምላክ እስራኤልን’ መረጠ። (ገላ. 3:26-29፤ 6:16) ይህ ብሔር ከአይሁድና ከአሕዛብ የተውጣጡ ቅቡዓን ክርስቲያኖችን ያቀፈ ጉባኤ ነው። (ኤፌ. 2:11-18) ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኋላም ቢሆን የእባቡ ዘር ለሴቲቱ ዘር ጠላትነት ማሳየቱን ቀጥሏል። የሮም መንግሥት በተለያየ ጊዜ የሴቲቱ ዘር ሁለተኛ ክፍል የሆነውን የክርስቲያን ጉባኤ ለማጥፋት ሙከራ አድርጓል።c
-
-
ይሖዋ ‘ሚስጥር ገላጭ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 15
-
-
a ይህች ሴት በሰማይ ያሉ መንፈሳዊ ፍጥረታትን ያቀፈችውንና በሚስት የተመሰለችውን የይሖዋን ድርጅት ትወክላለች።—ኢሳ. 54:1፤ ገላ. 4:26፤ ራእይ 12:1, 2
-
-
ይሖዋ ‘ሚስጥር ገላጭ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 15
-
-
c ሮማውያን በ70 ዓ.ም. ኢየሩሳሌምን ያጠፉ ቢሆንም ይህ ጥፋት በዘፍጥረት 3:15 ላይ የሚገኘው ትንቢት ፍጻሜ አይደለም። በዚያን ጊዜ ሥጋዊ እስራኤላውያን የአምላክ የተመረጠ ሕዝብ መሆናቸው ቀርቶ ነበር።
-