-
አምላክን መውደድ ሲባል ምን ማለት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1996 | ሰኔ 15
-
-
ወላጆቻቸው ፍጹም ተደርገው እንደተፈጠሩና የይሖዋ የመጀመሪያ ዓላማ ሰዎች ለዘላለም እንዲኖሩ መሆኑን ያውቁ ነበር። አዳምና ሔዋን ውብ ስለሆነው ኤደን ገነት ተርከውላቸውና እንዲህ ካለው ገነታዊ መኖሪያ የተባረሩበትን ምክንያት በሆነ መንገድ ነግረዋቸው ሊሆን ይችላል። ከዚህም በተጨማሪ ቃየንና አቤል በዘፍጥረት 3:15 ላይ የተመዘገበውን መለኮታዊ ትንቢት ያውቁት ይሆናል። ይሖዋ በዚህ ትንቢት አማካይነት እርሱን የሚወዱትንና ለእርሱ ያላቸውን ታማኝነት ያሳዩትን ሰዎች ለመጥቀም ሲል በተገቢው ጊዜ ነገሮችን እንደሚያስተካክል ያለውን ዓላማ ገልጿል።
ቃየንና አቤል ስለ ይሖዋና ስላሉት ባሕርያት ማወቃቸው የአምላክን ሞገስ የማግኘት ፍላጎት አሳድሮባቸው መሆን አለበት። በዚህ የተነሳ መሥዋዕት ይዘው ወደ ይሖዋ ቀረቡ። በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሰፈረው ታሪክ “ከብዙ ቀን በኋላም ቃየን ከምድር ፍሬ ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን አቀረበ፤ አቤልም ደግሞ ከበጎቹ በኩራትና ከስቡ አቀረበ” ይላል።—ዘፍጥረት 4:3, 4
-
-
አምላክን መውደድ ሲባል ምን ማለት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1996 | ሰኔ 15
-
-
ይሖዋ የቃየንን መሥዋዕት ያልተቀበለው ለምንድን ነው? በመሥዋዕቱ ላይ አንድ እንከን ነበረበትን? ይሖዋ በመሥዋዕቱ ያልተደሰተው ቃየን የእንስሳ መሥዋዕት ማቅረብ ሲገባው “ከምድር ፍሬ” ስላቀረበ ነውን? ለዚህ ላይሆን ይችላል። አምላክ ከጊዜ በኋላ እርሱን የሚያመልኩ ብዙ ሰዎች ያቀረቡለትን የእህልና የሌሎች የምድር ፍሬዎች መሥዋዕት በደስታ ተቀብሏል። (ዘሌዋውያን 2:1-16) ከሁኔታው ለመረዳት እንደሚቻለው በቃየን ልብ ውስጥ ተገቢ ያልሆነ ነገር ነበረ። ይሖዋ የቃየንን ልብ ማንበብ ከመቻሉም በተጨማሪ እንዲህ በማለት አስጠንቅቆት ነበር፦ “ለምን ተናደድህ? ለምንስ ፊትህ ጠቆረ? መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች፤ ፈቃድዋም ወደ አንተ ነው።”—ዘፍጥረት 4:6, 7
-