-
ሕይወት ያላቸው ነገሮች የተገኙት እንዴት ነው?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
5. ስለ ፍጥረት የሚገልጸው የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባ አሳማኝ ነው
መጽሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ 1 ላይ ምድርና በላይዋ ላይ ያለው ሕይወት ስለተገኙበት መንገድ ይገልጻል። ይህ ዘገባ እምነት የሚጣልበት ነው ወይስ አፈ ታሪክ? ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦
መጽሐፍ ቅዱስ ምድርና በላይዋ ላይ ያሉት ፍጥረታት ቃል በቃል በስድስት ቀናት ውስጥ እንደተፈጠሩ ያስተምራል?
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘው ስለ ፍጥረት የሚገልጸው ዘገባ አሳማኝና ምክንያታዊ እንደሆነ ይሰማሃል? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?
ዘፍጥረት 1:1ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦
ሳይንቲስቶች ሰማያትና ምድር መጀመሪያ እንዳላቸው ይናገራሉ። እነሱ የደረሱበት ድምዳሜ አሁን ካነበብነው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ጋር የሚስማማው እንዴት ነው?
አንዳንድ ሰዎች አምላክ ሕይወትን የፈጠረው በዝግመተ ለውጥ ተጠቅሞ ሊሆን እንደሚችል ያስባሉ። ዘፍጥረት 1:21, 25, 27ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አምላክ ውስብስብ ያልሆኑ ሴሎችን ከፈጠረ በኋላ እነዚህ ሴሎች በዝግመተ ለውጥ ዓሣዎችን፣ አጥቢ እንስሳትንና ሰዎችን እንዲያስገኙ እንዳደረገ ያስተምራል? ወይስ ሁሉንም ፍጥረታት የፈጠረው “እንደየወገናቸው” ነው?b
-