- 
	                        
            
            መጽናናትን ለማግኘት ይሖዋን ተስፋ አድርግመጠበቂያ ግንብ—1996 | ኅዳር 1
- 
                            - 
                                        5 በዚህ መንገድ ኃጢአተኞቹ ባልና ሚስት ወደ ሞት ማዝገም ጀመሩ። አምላክ በአዳም ላይ ሞት በፈረደበት ጊዜ እንዲህ ሲል አክሎ ተናግሮ ነበር፦ “ምድር ከአንተ የተነሣ የተረገመች ትሁን፤ በሕይወት ዘመንህም ሁሉ በድካም ከእርስዋ ትበላለህ፤ እሾህንና አሜከላን ታበቅልብሃለች፤ የምድርንም ቡቃያ ትበላለህ።” (ዘፍጥረት 3:17, 18) ስለዚህ አዳምና ሔዋን ያልለማውን ምድር ገነት ማድረግ የሚችሉበትን አጋጣሚ አጡ። ከኤደን በመባረራቸው ከተረገመችው ምድር ፍሬ ለማፍራት ጥረውና ግረው ለመሥራት ተገደዱ። ዘሮቻቸው ይህን የኃጢአተኝነትና የሞት ባሕርይ ስለወረሱ ማጽናኛ በሚያስፈልገው አስቸጋሪ ሁኔታ ሥር ወደቁ።—ሮሜ 5:12 
 
- 
                                        
- 
	                        
            
            መጽናናትን ለማግኘት ይሖዋን ተስፋ አድርግመጠበቂያ ግንብ—1996 | ኅዳር 1
- 
                            - 
                                        8 ይሖዋ ያን ክፉ ዓለም ምድር አቀፍ በሆነ የጥፋት ውኃ ለማጥፋት ወሰነ፤ በመጀመሪያ ግን ሕይወትን ለማዳን ሲል ኖኅን መርከብ እንዲሠራ አደረገው። በዚህ መንገድ የሰው ዘርና የተለያዩ የእንስሳት ዝርያዎች ከጥፋቱ ሊተርፉ ቻሉ። ኖኅና ቤተሰቡ ከጥፋቱ ውኃ በኋላ ከመርከቡ ውስጥ ወጥተው ወደ ጸዳችው ምድር ሲገቡ እንዴት ያለ እፎይታ ተሰምቷቸው ይሆን! በምድር ላይ ደርሶ የነበረው እርግማን ተወግዶ የእርሻ ሥራ ይበልጥ ቀላል ሆኖ ማግኘት ምንኛ የሚያጽናና ነው! በእርግጥም የላሜሕ ትንቢት ፍጻሜውን አግኝቷል፤ ኖኅም ከስሙ ትርጉም ጋር የሚስማማ ሥራ ሠርቷል። (ዘፍጥረት 8:21) ኖኅ የአምላክ ታማኝ አገልጋይ እንደ መሆኑ መጠን ለሰው ዘር መጠነኛ የሆነ “መጽናኛ” በማምጣት ረገድ የጎላ ሚና ተጫውቷል። ይሁን እንጂ ሰይጣንና አጋንንት መላእክቱ የሚያሳድሩት መጥፎ ተጽዕኖ ከጥፋት ውኃው ጋር አብሮ አልተወገደም፤ የሰው ዘርም በኃጢአት፣ በበሽታና በሞት ቀንበር በመቃተት ላይ ይገኛል። 
 
-