-
ሕይወት ያላቸው ነገሮች የተገኙት እንዴት ነው?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
3. የሰው ልጆችን ከእንስሳት የሚለያቸው ምንድን ነው?
ይሖዋ ምድርን ከፈጠረ በኋላ በምድር ላይ የሚኖሩ ሕይወት ያላቸውን ነገሮች ፈጥሯል። በመጀመሪያ ምድር በእንስሳትና በዕፀዋት እንድትሞላ አደረገ። ከዚያም “አምላክ . . . ሰውን በራሱ መልክ ፈጠረው።” (ዘፍጥረት 1:27ን አንብብ።) የሰው ልጆችን ልዩ የሚያደርጋቸው ምንድን ነው? የተፈጠርነው በአምላክ መልክ ስለሆነ እንደ ፍቅርና ፍትሕ ያሉ ባሕርያቱን ማንጸባረቅ እንችላለን። በተጨማሪም አምላክ የፈጠረን ቋንቋ የመማር፣ ውብ ነገሮችን የማድነቅና በሙዚቃ የመደሰት ችሎታ እንዲኖረን አድርጎ ነው። እንዲሁም ከእንስሳት በተለየ መልኩ እኛ ፈጣሪያችንን ማምለክ እንችላለን።
-
-
ሕይወት ያላቸው ነገሮች የተገኙት እንዴት ነው?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
6. የሰው ልጆች አምላክ ከፈጠራቸው ሌሎች ፍጥረታት ይለያሉ
ሰዎችንም ሆነ እንስሳትን የፈጠረው አምላክ ነው፤ ሆኖም ሰዎች ከእንስሳት የተለዩ ናቸው። ዘፍጥረት 1:26ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦
የተፈጠርነው በአምላክ መልክ ነው፤ ከዚህ አንጻር ፍቅርና ርኅራኄ የማሳየት ችሎታ ያለን መሆኑ ስለ አምላክ ባሕርይ ምን ይጠቁመናል?
-