የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ሕይወት ያላቸው ነገሮች የተገኙት እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 3. የሰው ልጆችን ከእንስሳት የሚለያቸው ምንድን ነው?

      ይሖዋ ምድርን ከፈጠረ በኋላ በምድር ላይ የሚኖሩ ሕይወት ያላቸውን ነገሮች ፈጥሯል። በመጀመሪያ ምድር በእንስሳትና በዕፀዋት እንድትሞላ አደረገ። ከዚያም “አምላክ . . . ሰውን በራሱ መልክ ፈጠረው።” (ዘፍጥረት 1:27⁠ን አንብብ።) የሰው ልጆችን ልዩ የሚያደርጋቸው ምንድን ነው? የተፈጠርነው በአምላክ መልክ ስለሆነ እንደ ፍቅርና ፍትሕ ያሉ ባሕርያቱን ማንጸባረቅ እንችላለን። በተጨማሪም አምላክ የፈጠረን ቋንቋ የመማር፣ ውብ ነገሮችን የማድነቅና በሙዚቃ የመደሰት ችሎታ እንዲኖረን አድርጎ ነው። እንዲሁም ከእንስሳት በተለየ መልኩ እኛ ፈጣሪያችንን ማምለክ እንችላለን።

  • ሕይወት ያላቸው ነገሮች የተገኙት እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 5. ስለ ፍጥረት የሚገልጸው የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባ አሳማኝ ነው

      መጽሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ 1 ላይ ምድርና በላይዋ ላይ ያለው ሕይወት ስለተገኙበት መንገድ ይገልጻል። ይህ ዘገባ እምነት የሚጣልበት ነው ወይስ አፈ ታሪክ? ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ ጽንፈ ዓለም የተገኘው በፍጥረት ነው?—ተቀንጭቦ የተወሰደ (3:51)

      ‘ጽንፈ ዓለም የተገኘው በፍጥረት ነው?—ተቀንጭቦ የተወሰደ’ ከተባለው ቪዲዮ የተወሰዱ ትዕይንቶች። 1. ስድስቱ የፍጥረት ቀናት ምድር ላይ ሆኖ ከሚመለከት ሰው አኳያ 2. ከስድስተኛው የፍጥረት ቀን በኋላ በምድር ላይ ፀሐይ፣ ደረቅ መሬት፣ ውኃ፣ ተክሎች፣ ወፎች፣ በመሬት ላይ የሚኖሩ እንስሳትና ሰዎች ይታያሉ
      • መጽሐፍ ቅዱስ ምድርና በላይዋ ላይ ያሉት ፍጥረታት ቃል በቃል በስድስት ቀናት ውስጥ እንደተፈጠሩ ያስተምራል?

      • በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘው ስለ ፍጥረት የሚገልጸው ዘገባ አሳማኝና ምክንያታዊ እንደሆነ ይሰማሃል? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?

      ዘፍጥረት 1:1⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ሳይንቲስቶች ሰማያትና ምድር መጀመሪያ እንዳላቸው ይናገራሉ። እነሱ የደረሱበት ድምዳሜ አሁን ካነበብነው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ጋር የሚስማማው እንዴት ነው?

      አንዳንድ ሰዎች አምላክ ሕይወትን የፈጠረው በዝግመተ ለውጥ ተጠቅሞ ሊሆን እንደሚችል ያስባሉ። ዘፍጥረት 1:21, 25, 27⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • መጽሐፍ ቅዱስ፣ አምላክ ውስብስብ ያልሆኑ ሴሎችን ከፈጠረ በኋላ እነዚህ ሴሎች በዝግመተ ለውጥ ዓሣዎችን፣ አጥቢ እንስሳትንና ሰዎችን እንዲያስገኙ እንዳደረገ ያስተምራል? ወይስ ሁሉንም ፍጥረታት የፈጠረው “እንደየወገናቸው” ነው?b

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ