-
‘የእስራኤልን ቤት የሠሩት’ እህትማማቾች ጭንቀትመጠበቂያ ግንብ—2007 | ጥቅምት 1
-
-
የልያ ልጅ ሮቤል እንኮይ ባገኘ ጊዜ፣ በራሔልና በልያ መካከል የነበረው የፉክክር መንፈስ በግልጽ ታይቷል። ይህ ፍሬ ለመጸነስ እንደሚረዳ ይታመን ነበር። ራሔል እንኮይ እንድትሰጣት ልያን ስትጠይቃት ልያ በምሬት “ባሌን የቀማሽኝ አነሰና የልጄን እንኮይ ደግሞ ልትወስጂ አማረሽ?” አለቻት። አንዳንዶች ይህ የልያ አነጋገር ያዕቆብ ከልያ ይልቅ ከራሔል ጋር ብዙ ጊዜ ያሳልፍ እንደነበር የሚጠቁም እንደሆነ ይሰማቸዋል። ራሔል፣ የልያ ቅሬታ ትክክል እንደሆነ ሳትገነዘብ አልቀረችም፤ በመሆኑም “ስለ ልጅሽ እንኮይ ዛሬ ከአንቺ ጋር ይደር” ብላ መለሰችላት። በዚህም ምክንያት ያዕቆብ ምሽት ላይ ቤቱ ሲገባ ልያ “በልጄ እንኮይ ስለ ተከራየሁህ የዛሬው አዳርህ ከእኔ ጋር ነው” አለችው።—ዘፍጥረት 30:15, 16
-
-
‘የእስራኤልን ቤት የሠሩት’ እህትማማቾች ጭንቀትመጠበቂያ ግንብ—2007 | ጥቅምት 1
-
-
ራሔል የወሰደችው እንኮይ እንድትጸንስ አልረዳትም። ካገባች ከስድስት ዓመታት በኋላ አርግዛ ዮሴፍ የተባለ ልጅ ልትወልድ የቻለችው ይሖዋ ‘ስላሰባትና’ ለጸሎቷ መልስ ስለሰጣት ነበር። ራሔል “እግዚአብሔር ዕፍረቴን አስወገደልኝ” ማለት የምትችለው በዚህ ጊዜ ነበር።—ዘፍጥረት 30:22-24
-