-
‘እንዴት ይህን ክፉ ድርጊት እፈጽማለሁ?’መጠበቂያ ግንብ—2014 | ኅዳር 1
-
-
ይህ ወጣት ተስፋ አልቆረጠም፤ ከዚህ ይልቅ ሥራውን በጥሩ ሁኔታ ማከናወኑን ቀጠለ። ይሖዋም ይህን ተመልክቶ የባረከው ሲሆን ዮሴፍ ብዙም ሳይቆይ በጌታው ፊት ሞገስ ማግኘት ቻለ። ጲጥፋራ የዮሴፍ ቤተሰቦች የሚያመልኩት ይሖዋ የተባለው አምላክ ይህን ወጣት እየባረከው እንደሆነ አስተዋለ፤ ለዮሴፍ የመጣው በረከት ደግሞ ለእሱም እንደተረፈ ጥርጥር የለውም። ዮሴፍ ቀስ በቀስ የጌታውን አክብሮት እያተረፈ ሄደ፤ እንዲያውም ጲጥፋራ በዚህ ጎበዝ ወጣት ላይ ከፍተኛ እምነት ስለጣለ ባለው ነገር ሁሉ ላይ ሾመው።—ዘፍጥረት 39:3-6
-
-
‘እንዴት ይህን ክፉ ድርጊት እፈጽማለሁ?’መጠበቂያ ግንብ—2014 | ኅዳር 1
-
-
ዘገባው በመቀጠል ዮሴፍ እያደገ እንደሄደ ይናገራል። ይህ ወጣት አድጎ “ጥሩ ቁመና ያለውና መልከ መልካም” ሰው ሆነ። እነዚህ ቃላት ዮሴፍ አደጋ ሊያጠላበት እንደሚችል ይጠቁማሉ፤ ምክንያቱም አካላዊ ውበት ብዙውን ጊዜ ተገቢ ያልሆነ ትኩረት ሊስብ ይችላል።
የጲጥፋራ ሚስት ታማኝ በሆነው በዮሴፍ ላይ ዓይኗን ጣለችበት
የጲጥፋራ ሚስት ታማኝ በሆነው በዮሴፍ ላይ ዓይኗን ጣለችበት
-