የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ከግብፅ ሃብት የሚልቅ ነገር
    መጠበቂያ ግንብ—2002 | ሰኔ 15
    • ወዲያው ማርያም ሮጣ ወደ ንግሥቲቱ መጣችና ‘ሕፃኑን እያጠባች የምታሳድግልሽ ከዕብራውያን ሴቶች መካከል ሞግዚት ላምጣልሽ?’ ስትል ጠየቀቻት። አንዳንዶች ይህንን ዘገባ ሲያነብቡ በጣም ይገረማሉ። የሙሴ እህት ያደረገችው ነገር ፈርዖን ዕብራውያንን “በዘዴ” በቁጥጥሩ ሥር ለማድረግ ከአማካሪዎቹ ጋር የሸረበውን ሴራ የሚጻረር ነበር። እርግጥ፣ የሙሴ ደህንነት የተመካው ንግሥቲቱ በእህቱ እቅድ በመስማማቷ ላይ ነበር። የፈርኦን ልጅ ‘እንድትሄድ’ ስትነግራት ማርያም ሮጣ ሄዳ እናቷን ጠራቻት። በመጨረሻም ዮካብድ በንጉሣዊ ቤተሰብ እንክብካቤ ሥር የገዛ ልጅዋን ለማሳደግ በደመወዝ ተቀጠረች።​​—⁠⁠ዘጸአት 2:​5-9

  • ከግብፅ ሃብት የሚልቅ ነገር
    መጠበቂያ ግንብ—2002 | ሰኔ 15
    • [በገጽ 11 ላይ የሚገኝ ሣጥን]

      ከሚያጠቡ ሞግዚቶች ጋር የሚደረግ ውል

      አብዛኛውን ጊዜ እናቶች የገዛ ልጆቻቸውን ያጠባሉ። ሆኖም ምሁሩ ብሬቫርድ ቻይልድስ ጆርናል ኦቭ ቢብሊካል ሊትሬቸር በተባለው ጽሑፋቸው ላይ እንደሚከተለው ብለዋል:- “አንዳንድ የባላባት [በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ] ቤተሰቦች አልፎ አልፎ ጡት አጥቢ ሞግዚት ይቀጥሩ ነበር። በተጨማሪም እናቲቱ ማጥባት ሳትችል ስትቀር ወይም ማንነቷ ሳይታወቅ ሲቀር ሕፃኑን እያጠባች የምታሳድግ ሞግዚት ትቀጠር ነበር። ሞግዚቷ በተሰጣት የጊዜ ገደብ ውስጥ ልጁን የማጥባትና የማሳደግ ኃላፊነት ነበረባት።” እያጠቡ ከሚያሳድጉ ሞግዚቶች ጋር የተደረጉ በርካታ ውሎች የሰፈሩባቸው ጥንታዊ ፓፒረሶች በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ ተገኝተዋል። እነዚህ መዛግብቶች ከሱመሪያን ዘመን አንስቶ በግብፅ ሰፍኖ የነበረው የግሪክ ባሕልና አስተሳሰብ እስከከሰመበት ዘመን ድረስ ተስፋፍቶ የነበረውን ልማድ ይጠቁማሉ። መዛግብቱ ከያዟቸው ዋና ዋና ሐሳቦች መካከል ውሉን የተዋዋሉት ሰዎች ያሰፈሯቸው ሐሳቦች፣ ውሉ የሚጸናበት ጊዜ፣ የሥራው ሁኔታ፣ ስለ አመጋገብ የተሰጡ ዝርዝር ሁኔታዎች፣ ውሉን አለማክበር ስለሚያስከትለው ቅጣት፣ ደመወዝና ደመወዙ ስለሚከፈልበት መንገድ የሚገልጹ ሐሳቦች ይገኙበታል። ቻይልድስ አብዛኛውን ጊዜ “ውሉ ለሁለት ወይም ለሦስት ዓመታት ይቆይ” እንደነበረ ገልጸዋል። “ሞግዚቷ ሕፃኑን ቤቷ ወስዳ ታሳድገዋለች። ሆኖም አንዳንድ ጊዜ የልጁን ደህንነት ለማረጋገጥ ሲባል ወደ ባለቤቱ እንድትመልሰው ትጠየቅ ነበር።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ