-
ዓይኖቻችሁ የሚመለከቱት ወዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018 | ሐምሌ
-
-
5-7. እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ ብዙም ሳይቆይ ምን ችግር ተከሰተ? ሙሴስ በዚህ ወቅት ምን አደረገ?
5 እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ ከሁለት ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ ገና ሲና ተራራ እንኳ ሳይደርሱ አንድ ከባድ ችግር ተከሰተ። ሕዝቡ ውኃ በማጣቱ ማማረርና በሙሴ ላይ ማጉረምረም ጀመረ። ሁኔታው በጣም እየተባባሰ ከመሄዱ የተነሳ ሙሴ “ይህን ሕዝብ ምን ባደርገው ይሻለኛል? ትንሽ ቆይተው እኮ ይወግሩኛል!” በማለት ወደ ይሖዋ ጮኸ። (ዘፀ. 17:4) ይሖዋም ግልጽ መመሪያዎችን ሰጠው። በትሩን ወስዶ በኮሬብ የሚገኘውን ዓለት ሲመታው ውኃ ከውስጡ እየተንዶለዶለ እንደሚወጣ ነገረው። ዘገባው “ሙሴም የእስራኤል ሽማግሌዎች እያዩ እንደተባለው አደረገ” ይላል። እስራኤላውያን እስኪበቃቸው ድረስ የጠጡ ሲሆን ችግሩም በዚህ መንገድ ተፈታ።—ዘፀ. 17:5, 6
-
-
ዓይኖቻችሁ የሚመለከቱት ወዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018 | ሐምሌ
-
-
11. ሙሴ ዓለቱን መምታቱ ይሖዋ ያከናወነው ነገር ተአምር እንዳይመስል አድርጎ ሊሆን የሚችለው እንዴት ነው?
11 ይሖዋ በሙሴ ላይ የተቆጣበት ሌላም ምክንያት ሊኖር ይችላል። በመጀመሪያው መሪባ አካባቢ የሚገኙት ዓለቶች ጠንካራ ጥቁር ድንጋዮች ናቸው። አንድ ሰው ጥቁር ድንጋይን የፈለገውን ያህል በኃይል ቢመታ ድንጋዩ ውኃ ያፈልቃል ብሎ የሚጠብቅ ማንም ሰው የለም። በሁለተኛው መሪባ አካባቢ ያሉት ዓለቶች ግን ከዚህ በጣም የተለዩ ሲሆኑ አብዛኛውን ጊዜ ያን ያህል ጥንካሬ የሌላቸው በሃ ድንጋዮች ናቸው። በሃ ድንጋይ በባሕርይው ውስጡ ክፍት ስለሆነ ይህ ድንጋይ ያለባቸው አካባቢዎች አብዛኛውን ጊዜ የተጠራቀመ የከርሰ ምድር ውኃ ይኖራቸዋል፤ በመሆኑም ሰዎች እነዚህን ድንጋዮች በመቦርቦር ውኃ ማውጣት ይችላሉ። ምናልባትም ሙሴ እንዲህ ያለውን ጥንካሬ የሌለው ዓለት ሁለት ጊዜ መምታቱ፣ ውኃው የፈለቀው በይሖዋ እርዳታ ሳይሆን በተፈጥሯዊ መንገድ ነው ለሚል ትችት አጋልጦት ይሆን? ሙሴ ዓለቱን ከመናገር ይልቅ መምታቱ፣ ተአምር የሆነው ነገር ተአምር እንዳይመስል አድርጎ ይሆን?b ይህን በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም።
-