-
“የይሖዋን አስተሳሰብ ያወቀ ማን ነው?”መጠበቂያ ግንብ—2010 | ጥቅምት 15
-
-
13. ኢየሱስ የሚያስብበትን መንገድ ማወቃችን የሚረዳን እንዴት ነው?
13 ኢየሱስ የሚያስብበትን መንገድ ማወቃችን በቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ለመረዳት ሊከብዱን የሚችሉ ታሪኮችን እንድንረዳ ያስችሉናል። ለምሳሌ ያህል፣ እስራኤላውያን የወርቅ ጥጃ ሠርተው ካመለኩ በኋላ ይሖዋ ለሙሴ ምን እንዳለው እንመልከት። እንዲህ ብሎ ነበር፦ “እነዚህን ሕዝብ አይቻቸዋለሁ፤ አንገተ ደንዳናዎችም ናቸው፤ አሁንም በእነርሱ ላይ፣ ቍጣዬ እንዲነድና እንዳጠፋቸው ተወኝ፤ ከዚያም አንተን ለታላቅ ሕዝብ አደርግሃለሁ።”—ዘፀ. 32:9, 10
14. ሙሴ ይሖዋ ለተናገረው ሐሳብ ምን ምላሽ ሰጠ?
14 ዘገባው ቀጥሎ እንዲህ ይላል፦ “ሙሴ የአምላኩን የእግዚአብሔርን ቸርነት ፈለገ፤ እንዲህም አለ፤ ‘እግዚአብሔር ሆይ በታላቅ ሥልጣንህና በኀያል ክንድህ ከግብፅ ባወጣኸው ሕዝብህ ላይ ቍጣህ ለምን ይነዳል? ግብፃውያን፣ “በተራራዎቹ ላይ ሊገድላቸው ከገጸ ምድርም ሊያጠፋቸው ስለ ፈለገ ነው ያወጣቸው” ለምን ይበሉ? ከክፉ ቍጣህ ተመለስ፤ ታገሥ፤ በሕዝብህም ላይ ጥፋት አታምጣ። ለባሪያዎችህ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለእስራኤል፣ “ዘርህን እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛዋለሁ፤ ለዘርህም ተስፋ አድርጌ የሰጠኋቸውን ይህችን ምድር ሁሉ እሰጣቸዋለሁ፤ ለዘላለምም ርስታቸው ትሆናለች” በማለት በራስህ የማልኸውን አስታውስ።’ ከዚያም እግዚአብሔር ታገሠ፤ በሕዝቡም ላይ አመጣባቸዋለሁ ያለውን ጥፋት አላመጣባቸውም።”—ዘፀ. 32:11-14a
15, 16. (ሀ) ይሖዋ የተናገረው ነገር ሙሴ ምን እንዲያደርግ አጋጣሚ ሰጥቶታል? (ለ) ይሖዋስ ምን አደረገ?
15 ይሖዋ አስተሳሰቡን እንዲያስተካክል ሙሴ ሐሳብ ማቅረቡ የግድ አስፈላጊ ነበር? በጭራሽ! ይሖዋ ምን ሊያደርግ እንደፈለገ ቢናገርም ይህ የመጨረሻ ውሳኔው አልነበረም። ኢየሱስ ፊልጶስንና ግሪካዊቷን ሴት እንደፈተናቸው ሁሉ ይሖዋም ሙሴን እየፈተነው ነበር ማለት ይቻላል። ሙሴ አመለካከቱን እንዲገልጽ አጋጣሚ ተሰጥቶት ነበር።b ይሖዋ፣ ሙሴን በእሱና በእስራኤል ሕዝብ መካከል አስታራቂ እንዲሆን የሾመው ሲሆን ሙሴ ይህን ኃላፊነት ለመወጣት የሚጫወተውን ሚናም አክብሮለታል። ከዚህም በተጨማሪ ይሖዋ ለማወቅ የፈለገው ነገር ነበር፦ ሙሴ በነገሩ መበሳጨቱ በሚሰጠው ምላሽ ላይ ተጽዕኖ ያሳድር ይሆን? ሙሴ ይህን አጋጣሚ በመጠቀም፣ ይሖዋ እስራኤላውያንን ትቶ የእሱን ዘሮች ታላቅ ሕዝብ እንዲያደርጋቸው ያበረታታው ይሆን?
-
-
“የይሖዋን አስተሳሰብ ያወቀ ማን ነው?”መጠበቂያ ግንብ—2010 | ጥቅምት 15
-
-
b አንዳንድ ምሑራን እንደሚሉት ከሆነ በዘፀአት 32:10 ላይ የሚገኘው “ተወኝ” የሚለው የዕብራይስጥ አገላለጽ ሙሴ ይሖዋንና እስራኤልን እንዲያስታርቅ ወይም ‘በመካከላቸው እንዲገባ’ የቀረበ ግብዣ እንደሆነ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። (መዝ. 106:23፤ ሕዝ. 22:30 የታረመው የ1980 ትርጉም) ይህ አስተያየት ትክክል ሆነም አልሆነ፣ ሙሴ አመለካከቱን ለይሖዋ ለመግለጽ ነፃነት እንደተሰማው መመልከት ይቻላል።
-