የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ምንጊዜም ጥሩነት አሳዩ
    መጠበቂያ ግንብ—2002 | ጥር 15
    • 10. በዘጸአት 34:​6, 7 NW ላይ የተጠቀሱት የይሖዋ ጥሩነት ገጽታዎች ምንድን ናቸው?

      10 ከአምላክ ቃል በምናገኘው መንፈሳዊ ብርሃንና በአምላክ ቅዱስ መንፈስ እርዳታ ‘ጥሩ የሆነውን ማድረጋችንን መቀጠል’ እንችላለን። (ሮሜ 13:​3 NW ) አዘውትረን መጽሐፍ ቅዱስን ስናጠና የይሖዋን ጥሩነት መምሰል የምንችለው እንዴት እንደሆነ ይበልጥ እየተማርን እንሄዳለን። ከዚህ በፊት የነበረው ርዕስ በዘጸአት 34:​6, 7 NW ላይ ተመዝግቦ በሚገኘውና ሙሴ በሰማው መግለጫ ላይ የተጠቀሱትን የአምላክ ጥሩነት አንዳንድ ገጽታዎች አብራርቷል። ጥቅሱ እንዲህ ይነበባል:- “ይሖዋ፣ ይሖዋ መሐሪ፣ ደግ፣ ለቁጣ የዘገየ፣ ፍቅራዊ ደግነቱና እውነቱ የበዛ፣ እስከ ሺህ ትውልድም ፍቅራዊ ደግነትን የሚጠብቅ፣ ስህተትና መተላለፍን ኃጢአትንም ይቅር የሚል፣ [በደለኛውን] ሳይቀጣ የማያልፍ . . . አምላክ ነው።” ይህንን የይሖዋ ጥሩነት መግለጫ በጥልቀት መመርመራችን ‘ጥሩ የሆነውን ማድረጋችንን እንድንቀጥል’ ይረዳናል።

  • ምንጊዜም ጥሩነት አሳዩ
    መጠበቂያ ግንብ—2002 | ጥር 15
    • 14. ይቅር ባይ መሆን የሚኖርብን ለምንድን ነው?

      14 አምላክ ለሙሴ የሰጠው መግለጫ ይቅር ባይ እንድንሆንም ሊያንቀሳቅሰን ይገባል። ምክንያቱም ይሖዋ ራሱ ይቅር ለማለት ዝግጁ ነው። (ማቴዎስ 6:​14, 15) እርግጥ ይሖዋ ንስሐ የማይገቡ ኃጢአተኞችን ይቀጣል። በመሆኑም የጉባኤውን መንፈሳዊ ንጽሕና መጠበቅን በተመለከተም የእርሱን የጥሩነት የአቋም ደረጃ ማክበር ይኖርብናል።​—⁠ዘሌዋውያን 5:​1፤ 1 ቆሮንቶስ 5:​11, 12፤ 1 ጢሞቴዎስ 5:​22

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ