-
ጎረቤትን መውደድ ሲባል ምን ማለት ነው?መጠበቂያ ግንብ—2006 | ታኅሣሥ 1
-
-
ባልንጀራዬ ማን ነው?
4. በዘሌዋውያን ምዕራፍ 19 መሠረት አይሁዳውያን እነማንን መውደድ ነበረባቸው?
4 ኢየሱስ በሁለተኛ ደረጃ የሚቀመጠው ትእዛዝ ጎረቤትህን እንደራስህ ውደድ የሚለው እንደሆነ ለፈሪሳዊው በነገረው ጊዜ ለእስራኤላውያን ተሰጥቷቸው የነበረውን አንድ ሕግ መጥቀሱ ነበር። ይህ ሕግ በዘሌዋውያን 19:18 ላይ ተመዝግቦ ይገኛል። በዚሁ ምዕራፍ ላይ አይሁዳውያን እስራኤላውያንን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሰዎችንም እንደ ባልንጀሮቻቸው ወይም ጎረቤቶቻቸው አድርገው እንዲመለከቷቸው ተነግሯቸዋል። ቁጥር 34 እንዲህ ይላል:- “አብሮአችሁ የሚኖረው መጻተኛ እንደ ገዛ ወገናችሁ ይታይ፤ እንደ ራሳችሁም ውደዱት፤ እናንተም በግብፅ መጻተኞች ነበራችሁና።” በመሆኑም አይሁዳዊ ያልሆኑትን ጭምር በተለይ ደግሞ ወደ ይሁዲነት የተለወጡ ሰዎችን በፍቅር መያዝ ነበረባቸው።
-
-
ጎረቤትን መውደድ ሲባል ምን ማለት ነው?መጠበቂያ ግንብ—2006 | ታኅሣሥ 1
-
-
ጎረቤትን መውደድ ሲባል ምን ማለት ነው?
8. ዘሌዋውያን ምዕራፍ 19 ፍቅር ማሳየት የሚቻልበትን መንገድ በተመለከተ ምን ይላል?
8 አምላክን መውደድ ተግባርን እንደሚጨምር ሁሉ ጎረቤትን መውደድም እንዲያው የስሜት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በድርጊትም የሚገለጽ ነው። የአምላክ ሕዝቦች ጎረቤቶቻቸውን እንደራሳቸው መውደድ እንዳለባቸው አበክሮ በሚገልጸው በዘሌዋውያን ምዕራፍ 19 ላይ በሰፈረው ትእዛዝ ዙሪያ ያለውን ሐሳብ ጠለቅ ብለን መመርመራችን ጠቃሚ ነው። በዚህ ምዕራፍ ላይ እስራኤላውያን መከር በሚሰበስቡበት ጊዜ ያገኙትን ምርት ለችግረኞችና ለመጻተኞች እንዲያካፍሉ መታዘዛቸውን እናነባለን። ስርቆት፣ ማታለልና ውሸት በእነርሱ ዘንድ ቦታ ሊኖራቸው አይገባም። ፍርድ ነክ በሆኑ ጉዳዮች ረገድ አድሎ ከመፈጸም መቆጠብ ነበረባቸው። አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ወንድሞቻቸውን መገሠጽ ይችሉ የነበረ ቢሆንም “ወንድምህን በልብህ አትጥላው” የሚል ቀጥተኛ ትእዛዝ ተሰጥቷቸዋል። እነዚህና ሌሎች በርካታ ትእዛዛት “ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ” በሚሉት ቃላት ሥር ተጠቃለዋል።—ዘሌዋውያን 19:9-11, 15, 17, 18
9. ይሖዋ እስራኤላውያንን ከሌሎች ብሔራት የተለዩ እንዲሆኑ ያዘዛቸው ለምንድን ነው?
9 እስራኤላውያን ሌሎችን መውደድ ያለባቸው ቢሆንም የሐሰት አማልክትን ከሚያመልኩ ሰዎች የተለዩ መሆን ነበረባቸው። ይሖዋ መጥፎ ወዳጅነት የሚያስከትለውን አደጋና መዘዝ በመንገር አስጠንቅቋቸዋል። ለምሳሌ ያህል፣ እስራኤላውያን ከሚወርሱት ምድር ያባረሯቸውን ሰዎች አስመልክቶ ይሖዋ እንዲህ የሚል ትእዛዝ ሰጥቷቸዋል:- “ከእነርሱ ጋር ጋብቻ አታድርግ፤ ሴት ልጆችህን ለወንድ ልጆቻቸው አትስጥ፤ ወይም ለወንድ ልጆችህ ሴት ልጆቻቸውን አታምጣ፤ ምክንያቱም እኔን ከመከተል ልጆችህን መልሰው ሌሎችን አማልክት እንዲያመልኩ ስለሚያደርጉና ከዚህም የተነሣ የእግዚአብሔር ቍጣ በላይህ ነዶ፣ ፈጥኖ ስለሚያጠፋህ ነው።”—ዘዳግም 7:3, 4
-